ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,102 የላብራቶሪ ምርመራ 109 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3,630 ደርሷል።

ቫይረሱ የተገኘባቸው 60 ወንድ እና 49 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ1 እስከ 78 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው።

ቫይረሱ የተገኘባቸው 81 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 9 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 4 ሰዎች ከሱማሌ ክልል፣ 4 ሰዎች ከደቡብ ክልል፣ 3 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 3 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣ 3 ሰዎች ከአፋር ክልል እና 2 ሰዎች ከሐረሪ ክልል ናቸው።

ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርመራ ውስጥ 20 (5 ከጤና ተቋም እና 15 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ሲሆን የ45 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ነዋሪ ሴት ከማህበረሰቡ በተወሰደ ናሙና የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባታል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸውና ህይወታቸው የለፈ ሰዎች ቁጥር ስልሳ አንድ (61) ደርሷል።

@TenaET | https://tena.et/update

Comments

Be the first to add a comment